Tuesday, November 16, 2010

የተዋሕዶ አርበኞች መልክት

                በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
      የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን  አርበኞች ከተቋቋመ ረዘም ያለ ጊዜ ያሳለፈ ሲሆን በሀረሪቱ በሰፈነው ህገወጥ  የመንግስት ስርአት የተነሳ በቅድስት ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና ተከታዮቿ ላይ ብዙ ችግሮች በመድረሳቸውና አሁንም በከፍተኛ ደረጃ እየደረሱ ናቸው፡፡ ከችግሮቹ መሀል፡-
1-      በቤተክርስቲያን አስተዳደር ላይ ጣልቃ በመግባት ያለ ህዝቡ ፍቃድ በጉልበት ጳጳስ በመሾም የቤተክርስቲያንን   አስተዳደርን በመቆጣተር ቤተክርስቲያንንና ክርስቲያኖችን የእምነት ነፃነት አሳጥቷል፡፡
2-    መንግስት በሚያራምደው የዘረኝነት ፖሊሲ እና በ1928 ዓ.ም ጣልያን ሀገራችንን በወረረበት ወቅት ክርስቲያኖችን ለማዳከም ክልሎችን ባካለለበት መልኩ በመካለላቸው፡የተነሳ፤ በቤተክርስቲያን እና በአማኞቿ ላይ ከፍተኛ ችግር እየደረሰ በመሆኑ፡፡
3-    አነስተኛ ክርስቲያኖች በሚኖሩበት አካባቢ ኣማኞች ላይ በተደጋጋሚ የሚደርስ የመብት ገፈፋ ፣ግድያ፣ ድብደባ፣ እስራት፣ የቤተክርስቲያን ቃጠሎና፣ የንብረት ዘረፋ፡፡
4-    አክራሪነት በሚሰማቸው እስላሞች እና ጸረ ኦርቶዶክስ አቋም ባላቸው የመንግስት ባለስልጣናት አማካኝነት፤ ያላግባብ የክርስቲያኖችንና የቤተክርስቲያንን መሬት መንጠቅ፣ ከመንግስት ስራዎች ማባረር፣ ያላግባብ ማሰር መደብደብ እና መግደል፡፡ በተጨማሪም ጸረ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅስቀሳ ማድረግ፡፡
5-    በከፍተኛ ደረጃ የቤተክርስቲያን ቅርስ ላይ የሚደርሱ ዘረፋዎችና ውድመቶች፡፡
6-    በውስጥም ሆነ በውጭ የሚንቀሳቀሱ በዘር ፖለቲካ ሽፋን  የሚደረግ ጸረ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ፡፡
7-    በፖለቲካ፣ በሀይማኖት እና በኢኮኖሚ ምክንያት ጸረ ኢትዮጵያ አቋም ባላቸው አረብ ሀገራት የሚደገፉ እክራሪ ሀይላት በሀገሪቱ እና በጐረቤት ሀገራት መስፋፋት፡፡ የመሳሰሉት ችግሮች እየደረሱ ይገኛሉ፡፡
       ይህንን በተመለከት በመጋቤት 16 ቀን 1997ዓ.ም በምኒልክ ጋዜጣ መልእክታችንን ለመንግስት አስተላልፈን ነበር፤ መንግስት ችግሩን ሊፈታ ባለመቻሉ በጋዜጣው ላይ ለመንግስት አዳስጠነቀቅነው ሁሉ ለቤተክርስቲያናችን ነጻነት እና ወገኖቻችንን ከመከራ ለመታደግ እግዚአብሔር ሀይል በማድረግ በማንኛውም መንገድ እየተንቀሳቀስን እንገኛለን፡፡ ማንኛውም የተዋህዶ ክርስትያን የተዋህዶ አርበኛችን አላማ መደገፍ ሀይማኖታዊ ግዲታ መሆኑ አውቆ
ለእንቅስቃሴው  ማንኛውንም አይነት ድጋፍ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
        ‹‹ወደ ሞት የሚነዱትን ታደግ ሊታረዱ የተወሰኑትን አድን፡፡ እንሁ ይህን አላውቅም ብትል፤ ልቦችን የሚመረምር እርሱ አያስተውልምን፤ ነፍስህንም የሚመለከት እርሱ አያውቅምን ለሰው ሁሉ እደስራው አይመልስለትምን፡፡ ››
            መጽሐፈ ምሳሌ  ም.24 ቁ. 11