Saturday, October 28, 2017

ሰማእትነት አያምልጥህ

ለመላው አዲስ አበባ ዙሪያና የንደር ነዋሪ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን የቀረበ ብጹአን መነኮሳትን ከእስር የማስፈታት ጥሪ!
v  “ በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችሗል ይገድሉአችሁማል ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።”  የማቲዎስ ወ. ም-24፣ቁ-9
               
 
 
 
           ፍጹም ልትሆን ብትፈልግ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ሰተህ ተከተለኝ ፤ በሚለው አምላካዊ ትዛዝ መሰረት ሀብትና ንብረታቸውን እና ቤተሰባቸውን ትተው በታላቁ ዋልድባ ገዳም መንነው በፆም እና በፀሎት የፀኑትን ብጹአን አባቶች ገዳማችን የመፍረስ አደጋ አጋጥሞታል ብለው ለምእመናኑ በማሳወቃቸው ምክንያት በንደር እና በአዲስ አበባ ቂሊንጦ እስር ቤት በመሰቃየት ላይ ናቸው። በአዲስ አበባ  እና በንደር የምትኖሩ ምእመናን እደቀደሙት ሰማእታት አባቶቻችሁ ሰማእትነት ለመቀበል ከዚህ የተሻለ እድል አታገኙም። በዚሁ መሰረት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሰማህ ላልሰማ እያሳወክ እንደጥምቀት እና መስቀል በነቂስ በመውጣት አዲስ አበባ ወደ ቂሊንጦ እና  ንደር እስርቤት በመትመም ብጹአን መነኮሳትን እንድናስፈታ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ኅብረት ጥሪ ቀርቦልሀል።
 
v  “ ወደ ሞት የሚነዱትን ታደግ ሊታረዱ የተወሰኑትን አድን። እንሆ ይህን አላውቅም ብትል፤ ልቦችን የሚመረምር እርሱ አያስተውልምን? ነፍስህንም የሚመለከት እርሱ አያውቅምን? ለሰውስ ሁሉ እንደ ስራው አይመልስለትምን?  መጽሐፈ ምሳሌ ም.29 ቁ.11
 
 
 


Sunday, April 2, 2017

በኢሕአዲግ ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የደረሰ የዘር ፍጅትና ጥቃት


 

      ኢሕአዲግን የመሰረቱት ግለሰቦች አስቀድመው በ1960ቹ ዓ.ም በተማሪው እንቅስቃሴ ወቅት የማርክስ ሌኒን የፖለቲካ አማኝ የነበሩ የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ፤ በዚሁ እምነት መሰረት በፀረ ሀይማኖትን አስተሳሰብ በመለከፋቸው በተለይ ለኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ጥላቻ አላቸው። ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን እና ተከታዮችን በሀገሪቱ ብቸኛ ተጠቃሚ አድርጎ የሚሰብከው  የ1960ዎቹ የነበረ ዋለልኝ መኮንን የሚባለው ወጣት (The Question of Nationalities in Ethiopia) በሚለው የእንጊልዘኛ ጽሑፉ ላይ በጊዜው የነበሩ ወጣቶች ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ጥላቻ  እንደነበራቸው ያሳያል።
       በጽሑፍ ላይ እንደታየው ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እና ተከታዮቿ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም አይነት የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ የበላይነት ሊኖራቸው እንደማይገባ ይሰብካል። ይህን የወያኔን ጸረ ኦርቶዶክስ አቋም ምቹ ሁኔታ የፈጠረላቸው ጸረ ኦርቶዶክስ ፕሮቴስታንት እና ሙስሊም ባለስልጣናት ስልጣናቸውን በመጠቀም በኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ላይ ከፍተኛ የዘር ፍጅት ፈጽመዋል።  በተግባር እንደሚታየው ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ከፖለቲካው ስርአት በተቀነባበረ መልኩ ሲገለሉ በኢኮኖሚውም እረገድ በአዋጅ ንብረታቸውን ተወርሰው አብዛኛውም ምእመናን በድሕነት እንዲማቅቁ ተደርገው በራሳቸው መሬትና ባፈሩት ንብረት ሌሎች ሲንደላቀቁበት ይታያል።
 
 


 
       (Marxism and the National Question by J.V. Stalin) መጽሐፍ ላይ እንደሚለው “የአንድን ሀገር ሕዝብ እንድ ከሚያደርጋቸው ነገር አንዱ ተመሳሳይ ቋንቋ ተናጋሪዎች መሆናቸው ነው” ይላል፤ ወያኔ ይህንን አስተሳሰብ በመከተል በኢትዮጵያ ውስጥ የቋንቋ ማንነት ከሌላው ማንነት በተለየ የበላይ አድርጎ በመስበክ የብዙ ቋንቋ ተናጋሪ ሀገር ኢትዮጵያን እንደ አንድ ሀገር ባለመቁጠር በኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ ያልነበረ ቋንቋን መሰረት ያደረገ ስርአት መንግስትና ሀገር ለማስፈን እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

         ከላይ የተጠቀሰውን አላማውን ለማሳካት በዋናነት የሀይማኖት አንድነት እና ሕብረት እንቅፈት እንደሆኑበት ተገንዝቧል። በዮሐንስ ራእይ ም.13 ከ ቁ.6 እንዲሕ ተብሎ እንደተጸፈው “ እግዚአብሔርንም ለመሳደብ ስሙንና ማደሪያውንም በሰማይም የሚያድሩትን ሊሳደብ አፍን ከፈተ። ቅዱሳንንም ይዋጋ ዘንድ ድልም ያደርጋቸው ዘንድ ተሰጠው በነገድና በወገንምበቋንቋም በሕዝብም ሁሉ ላይ ስልጣን ተሰጠው። ከዓለምም ፍጥረት ጀምሮ በታረደው በግ ሕይወት መጽሐፍ ስማቸው ያልተጻፈ በምድር የሚኖሩ ሁሉ ይሰግዱለታል። ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ።”  ይሕ የሚያሳየን የዳቢሎስ መንፈስ በመሪዎች ላይ በማደር በቋንቋና በነገድ እየከፈለ ያልተጠመቁትንና የክርስቶስን ስጋና ደሙን ያልተቀበሉትን እንደሚገዙለትና ክርስትናን ተቀብለው ነገር ግን በቋንቋና በነገድ ወገንተኝነት የሳቱትና ለዳብሎስ የተገዙለት ስማቸው ከሕይወት መጽሐፍ እንደሚደመስ ነው።
        ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሰው ልጅ በዘሩ፣ በቋንቋው፣ በባሕሉ፣ እና በሀገሩ የተለያየ ማንነት ቢኖረውም የሀይማኖቱ ማንነት ከሁሉ የበለጠ ማንነት ነው ብላ ታስተምራለች። ይህንንም እምነት የማያምን ክርስቲያን ክርስቲያን ተብሉ አይጠርም፤ እራሱንም ከክርስቲያን ሕብረት የወጣና የተለየ ይሆናል። ይህ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነትና ሕግ በዳብሎስ መንፍስ ለሚመራው የወያኔ መሪዎች እራስ ምታት ስለሆነባቸው ገና ጫካ ሳሉ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጠላት አድርገው በመውስድ ከቻሉ በቀጥታ የጥፋት እርምጃ በመውሰድ ካልቻሉ ከቤተክርስቲያን በእምነታቸው የተለዩና የተወገዙ አፍቃሪ ካቶሊኮችን በቤተክርስቲያን አስርጎ በማስገባት ከፍተኛውን የመንፈሳዊ አስተዳደር ቦታ በማስያዝ ቤተክርስቲያንን አቅም አልባና ደካማ በማድረግ እና ምእመናኑ ለመንግስት እንዲገዙ አድርገዋል።
       ዛሬ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በሕውሀት ስር በመሆኑ የቤተክርስቲያን ንብረት በመዝረፍ እና እውነተኛ ምእመናንን በማሳደድ ላይ ይገኛል። ሊላው ሕውሀት የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን  እና ምእመናንን ጠላት አድርጎ በመውሰዱ ምእመናንን በተለያየ ጊዜ የተለያየ ስም በመስጠት የጭፍጨፋ እርምጃ በተቀነባበረ መልኩ ተወስዶበታል እየተወሰደም ይገኛል።
 
 
 

          በፈረንጆች አቆጣጠር በ1994 በኢትዮጵያ ከጠቅላላው የሕዝቡ ቁጥር 50.6 % ኦርቶዶክስ ክርስቲያን የነበረ ሲሆን ከ 13 ዓመት በሆላ በተደረገ የሕዝብ ቆጠራ በ2007 በ 7.1% አንሶ 43.5% ሆኖል ልዩነቱን በቁጥር ስንቀይረው 2282973 ብዛት ያለው ሕዝብ ይሆናል ይህም የሆነው ወያኔ ስልጣን ከያዘ ከ3 ዓመት የጀምሮ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ1986 – 1999 ዓ.ም ሲሆን በነዚ ጊዜያቶች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ   የጅምላ ጭፍጨፋ፣ እስራት፣ ከመሬቱ ማፈናቀል፣ የመሳሰሉት እርምጃዎች ሁሉ የተወሰዱበት ጊዝያት ነበሩ።
 

 

 




 





       ለምሳሌ ቦታዎችን ብንጠቅስ፦ የእስልምና የክልል ባለስልጣናትን በመጠቀም በሐረር፣ በቤንሻንጉል፣ እና በአርሲ፤ የፕሮቴስታንት እና የካቶሊክ የክልል ባለስልጣናትን በመጠቀም በወለጋ እና በጉራ ፈርዳ ላይ የተደረጉት ጭፍጨፋዎችና ማፈናቀሎች በሙሉ በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የተፈፀሙ ናቸው። ይህንን እውነታ የሚያጠናክር በ1994 እና በ2007 በሀገሪቱ በዋና ዋና ክልሎች የእምነቶች አማኝ ቁጥር በፐርሰንት እንደተቀመጠው የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ቁጥር በከፍተኛ ቁጥር  እንዳሽቆለቆለ በቂ ማሳያ ነው።


 

Saturday, November 5, 2016

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ፖለቲካ

    - የቀድሞ የኢትዮጵያ ስርአተመንግስት እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
    - የጣልያን ወረራ እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
    - የአፄ ኃ/ሥላሴ መንግስት እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
    - ማርክስ ሌኒስት የፀረ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ
    - የደርግ መንግስትና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
    - የሕወሀት ፖለቲካና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
    - የኢትዮጵያ ሙስሊሞችና የሕውሀት ጠብ
    - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች የነጻነት ትግል እና የፓለቲካ ስልጣን ጥያቄ
         ኢትዮጵያ ቡዙ አይነት ባሕል እና የተለያዩ ቋንቋ የሚነገሩባት በዋናነት ክርስትና እና እስልምና እንዲሁም የተለያዩ እምነቶች ተከታይ ሕዝቦች ያሉባት ሀገር ናት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች እስካሁንም ድረስ በቁጥር ብዛት በሀገሪቱ ከፍተኛውን ቦታ ይይዛሉ።





-    የቀድሞ የኢትዮጵያ ስርአተመንግስት እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
      በኢትዮጵያ የመንግሰት ስርአት ከክርሰትና በፍት  የቆየ ሲሆን የንጉሰ ነገስቱ ሀይማኖት ክርስትናን ከተቀበለበት ጊዜ አንስቶ ነገስታቱ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን በማስፋፋት ትልቅ ሚና ነበራቸው። የክርስትና ህግጋትና አስተምሮ በመንግስት ስርአት እና ባሕል ውስጥ ተዋሕደው ይታያሉ።



-    የጣልያን ወረራ እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን

       በ1928 ዓ.ም ጣልያን ኢትዮጵያን ሲወር  ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከመንግስት ጋር ያላትን ቁርኝት በሚገባ ስለተረዳ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን በጠላትነት በመፈረጅ፤ ቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

               በጠቅላላው ፋሺስት ኢጣልያ በአምስት አመት ወረራው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ  ክርስቲያኖች፣ ካህናት፣ መነኮሳት ላይ ያደረሰው ጭፍጨፋ እጅግ ዘግናኝ ነበር፡፡ በመነኮሳት ላይ እና በካህናት ላይ ብቻ  የደረሰውን   ስንመለከት፤

1.   በሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም አቡነ ጴጥሮስ በ አ.አ ከተማ ተገደሉ፡፡

2.   በኅዳር 24 ቀን 1929 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል በጎሬ ላይ ታረዱ፡፡

3.   ግንቦት 23 ቀን 1929 ዓ.ም የዜና ማርቆስ ካህናት በቅዳሴ ላይ እንዳሉ 43 መነኮሳት ተገድለዋል፡፡

4.   በሰኔ 12 ቀን 1929 ዓ.ም የዝቋላ ገዳም መነኮሳት በማስታኮት ላይ እንዳሉ 211 መነኮሳት ታረዱ ፡፡

5.   በሰኔ 3 ቀን 1929ዓ.ም የምድረ ከብድ ገዳም 60 መነኮሳት ታረዱ፡፡

6.   በሰኔ 15 ቀን 1929 ዓ.ም የአሰቦት ደብረ ወገግ መነኮሳት 91 ታረዱ፡፡

7.   በኅዳር 25 ቀን 1929 ዓ.ም የአዲስ ዓለም ካህናት በአሰቃቂ ሁኔታ ታረዱ ብዛታቸው 135 ነበር፡፡

8.   ጥቅምት 17 ቀን 1929 ዓ.ም በደብረ ዳሞ ገዳም 416 መነኮሳት ታርደዋል፡፡

9.   መጋቢት 16 ቀን 1929 ዓ.ም የማህበረ ሥላሴ ገዳም መነኮሳት ጠባቂዎች ሳይቀሩ 513 ተገደሉ በዚህም ቀን የደብረ አባይ ገዳም ተመዘበረ፡፡

10. በሚያዝያ 18 እና 20 ቀን 1929 ዓ.ም የመርጦለማርያምና የተድባበ ማርያም ካህናት 363 በጭካኔ ታረዱ፡፡

11. በሐምሌ 29 ቀን 1929 ዓ.ም የጎንደር ሊቃውንት ተለቅመው ከታሰሩ በኃላ ግማሾቹ ተገደሉ የተቀሩት ወደእስር ተወሰዱ፡፡

12. የካቲት 18 ቀን 1929 ዓ.ም የየካ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታላላቅ 11 ሊቃውንት ተጠርተው ስቃይ ወዳለበት ቦታ ተወሰደው ታሠሩና ግማሾቹ ተገደሉ፡፡ 

                  ይህ በታላላቅ ደብራትና ገዳማት ላይ የተፈጸሙ እና ተመዝግበው የሚታወቁ ሲሆኑ ሳይመዘገቡ የቀሩ ብዙ እንዳሉ የሚገመት ሲሆን የሟቾቹም ቁጥር ከዚህም ይበልጣል፤ ከዚህም ጋር  በተያያዘ  በአምስት ዓመት  ውስጥ  ከ2000  በላይ  ቤተክርስቲያናት  ተቃጠልዋለል፡፡

       ፋሺስት ኢጣልያ በተከተላው የከፋፍለ ግዛ ፖሊው የእስልምና ተከታይ ኢትዮጵያውያንን ከክርስቲያኑ የኢትዮጵያ መንግስት ነፃ ለማውጣት የመጣ አድርጎ ይሰብክ ስለነበር በወቅቱ ስብከቱን ያመኑ 12ሺ የሙስሊም ጦር ከጎኑ ማሰለፍ ችሎ ነበር።


-    የአፄ /ላሴ መንግስት እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን

       አፄ ኃ/ላሴ አፍቃሪ ምእራባውያን በመሆናቸው የተነሳ ኢትዮጵያን በተራማጅ እስተሳሰብ መርቶ ሕዝቡን ምእራባዊ ባሕል፣ እምነት እና አስተሳሰብ እንዲኖረው ገና እልጋ ወራሽ ከነበሩበት ጊዜ አንስቶ ሲሰሩበት ነበር። በጊዘው ለነበረው የአለም መንግስታት ማሕበር ኢትዮጵያን አባል ለማረግ በፈረንሳይ ቋንቋ በድብቅ በጻፍት ደብዳቤ ላይ ለረጅም ጊዜ የኖረውን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከመንግስት ግኑኝነት እንደሚነጥሉ ቃል በመግባት ነበር።

      አፄ /ላሴ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በስም እንዳለች ሆና ስርአቷ ግን ፍፁም የካቶሊክን መንገድ እንድትከተል እንዳደረጉ ብዙ አባቶች ይናገራሉ። ለዚህም ማስረጃ   አፄ /ስላሴ  ስልጣን ከያዙ በሆላ የተገነቡ ቤተክርስቲያናት እና የቤተክርስቲያናት ስእላት ካቶሊካዌ ሆነዋል።

          ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እራሷን ችላ ጳጳሳትን እንድትሾም እና ሲኖዶስ እንዲኖራት የተሰራው ስራ ችግሮች የሞሉትና አንዳዶቹ የቤተክርስቲያንን ስርአት የጣሱ ናቸው። ለምሳሌ፦ ሐዋርያት በ(ሐዋርያት ስራ ም. 6 ቁ.2-6) እንዳዘዙት ጳጳስቱ በቤተክርስቲያኖ ውስጥ የመንፈሳዊውን ስራ ብቻ መስራት ሲገባቸው፤ የቤተክርስቲያን ስጋዌ ስርዎች በምእመናን በተመረጡ ሰዎች መሰራት ሲገባው ትዛዙን ወደጎን በመተው ጣልቃ ገብተዋል። እንዲሁም ሐዋርያትን የሚወክሉ ብፁዐን ጳጳሳት ለአገልግሎታቸው የደሞዝ ክፍያ እንዲኖራቸው መደረጉ በማቴዎስ ወንጌል ም.19 ቁ.21-22 እንደተጻፈው “ ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂድና ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ መጥተህም ተከተለኝ” የሚለውን የእግዚአብሔርን ቃል የጣሰ ነው።   

      በአጠቃላይ አፄ  ኃ/ላሴ በዘመናዌ ትምሕርት ሰበብ ትውልዱን የሀገሩን ታሪክ፣ ማንነቱን እና ሀይማኖቱን እንዳያውቅ በመደረጉ በተለይ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንድትዳከም ሆኖዋል።


-    ማርክስ ሌኒስት የፀረ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ

       የማርክስ ሌኒስት አዲሱ ሪወትአለም ሀይማኖትን በፅኑ የሚቃወም እንደመሆኑ በሌሎች ሀገራት እንደታየው ሁሉ በኢትዮጵያም ሀይማኖትን የእድገት ጸር አድርጎ ፈርጇል፤ በተለይ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን እና ተከታዮችን በሀገሪቱ ብቸኛ ተጠቃሚ አድርጎ የሚሰብከው  የ1960ዎቹ የነበረ ዋለልኝ መኮንን የሚባለው ወጣት (The Question of Nationalities in Ethiopia) በሚለው የእንጊልዘኛ ጽሑፉ ላይ በጊዜው የነበሩ ወጣቶች ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ጥላቻ  እንደነበራቸው ያሳያል።

       በጽሑፍ ላይ እንደታየው ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እና ተከታዮቿ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም አይነት የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ የበላይነት ሊኖራቸው እንደማይገባ ይሰብካል። ለዚም ይመስላል አሁን በተግባር እንደሚታየው ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ከፖለቲካው ስርአት በተቀነባበረ መልኩ ሲገለሉ በኢኮኖሚውም እረገድ በአዋጅ ንብረታቸውን ተወርሰው አብዛኛውም ምእመናን በድሕነት እንዲማቅቁ ተደርገው በራሳቸው መሬትና ባፈሩት ንብረት ሌሎች ሲንደላቀቁበት የሚታየው።


-    የደርግ መንግስትና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን

      የደርግ መንግሰት የፀረ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስብከት ሰለባ የሆነ ስርአት ሲሆን፤ በቀጥታና በግልጽ ቤተክርስቲያኗ ላይ እና ምእመናንኑ ላይ ከፍተኛ በደል አድርሷል። ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመሬት ይዞታና የነበራትን ንብረቶች ከመዝረፍ አልፎ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን በጠላትነት በመፈረጅ በኢኮኖሚ ለማደሕየት መሬታቸውን፣ መኖርያ ቤታቸውን እና ሕንጻዎቻቸውን በተቀነባበረ መልኩ ዘርፋል። አድሀሪ እና ፀረ አብዮት ብሉ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን በመፈረጅ ከፍተኛ የጅምላ ፍጅት  ፈጽሟል።


-    የሕወሀት ፖለቲካና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን

      ሕውሀትን የመሰረቱት ግለሰቦች አስቀድመው በ1960ቹ ዓ.ም በተማሪው እንቅስቃሴ ወቅት የማርክስ ሌኒን የፖለቲካ አማኝ የነበሩ የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ፤ በዚሁ እምነት መሰረት በፀረ ሀይማኖትን አስተሳሰብ በመለከፋቸው ለኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ጥላቻ አላቸው። (Marxism and the National Question by J.V. Stalin ) መጽሐፍ ላይ እንደሚለው “የአንድን ሀገር ሕዝብ እንድ ከሚያደርጋቸው ነገር አንዱ ተመሳሳይ ቋንቋ ተናጋሪዎች መሆናቸው ነው” ይላል፤ ይህንን አስተሳሰብ በመከተል በኢትዮጵያ ውስጥ የቋንቋ ማንነት ከሌላው ማንነት በተለየ የበላይ አድርጎ በመስበክ የብዙ ቋንቋ ተናጋሪ ሀገር ኢትዮጵያን እንደ አንድ ሀገር ባለመቁጠር በኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪክ ያልነበረ ቋንቋን መሰረት ያደረገ ስርአት መንግስትና ሀገር ለማስፈን እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

      ከላይ የተጠቀሰውን አላማውን ለማሳካት በዋናነት የሀይማኖት አንድነት እና ሕብረት እንቅፈት እንደሆኑበት ተገንዝቧል፤ በተልይ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሰው ልጅ በዘሩ፣ በቋንቋው፣ በባሕሉ፣ እና በሀገሩ የተለያየ ማንነት ቢኖረውም የሀይማኖቱ ማንነት ከሁሉ የበለጠ ማንነት ነው ብላ ታስተምራለች። ይህንንም እምነት የማያምን ክርስቲያን ክርስቲያን ተብሉ አይጠርም፤ እራሱንም ከክርስቲያን ሕብረት የወጣና የተለየ ይሆናል። ይህ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነትና ሕግ ለሕውሀቶች እራስ ምታት ስለሆነባቸው ገና ጫካ ሳሉ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጠላት አድርገው በመውስድ ከቻሉ በቀጥታ የጥፋት እርምጃ በመውሰድ ካልቻሉ ከቤተክርስቲያን በእምነታቸው የተለዩ አፍቃሪ ካቶሊኮችን በቤተክርስቲያን እስርጎ በማስገባት ከፍተኛውን ቦታ በማስያዝ ቤተክርስቲያንን አቅም አልባና ደካማ በማድረግ እና ምእመናኑ ለወያኔ ስርአት እንዲገዙ አድርገዋል።

      ዛሬ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በሕውሀት ስር በመሆኑ የቤተክርስቲያን ንብረት በመዝረፍ እና እውነተኛ ምእመናንን በማሳደድ ላይ ይገኛል። ሊላው ሕውሀት የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን  እና ምእመናንን ጠላት አድርጎ በመውሰዱ ምእመናንን በተለያየ ጊዜ የተለያየ ስም በመስጠት የጭፍጨፋ እርምጃ በተቀነባበረ መልኩ ተወስዶበታል እየተወሰደም ይገኛል። ሕውሀት ለ25 ዓመት ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን ሲጨፈጭፍ የተለያዩ የማደናገሪያ ዘዲዎችን በመጠቀም ሲሆን ከነዚሁስጥም ሁለቱን እንደሚከተለው ቀርቦል፦

1-      ከጠቅላላው የሕዝቡ ቁጥር 81.5 % ኦርቶዶክስ የሆነውን የአማራውን ሕዝብ ማጥፋት ኦርቶዶክስን ማጥፋት ነው በማለት የጅምላ ጭፍጨፋ፣ እስራት፣ ከመሬቱ ማፈናቀል፣ የመሳሰሉት እርምጃዎች ሁሉ ተወስደዋል እየተወሰዱም ይገኛሉ። ይህንን እውነት የሚያጠናክርልን በአማራ ስም ጭፍጨፋ በተደረጉባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ሁሉ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናትም ተቃጥለዋል አገልጋይ ካሕናትም ታርደዋል።

ለምሳሌ ቦታዎችን ብንጠቅስ፦ የእስልምና የክልል ባለስልጣናትን በመጠቀም በሐረር፣ በቤንሻንጉል፣ እና በአርሲ፤ የፕሮቴስታንት እና የካቶሊክ የክልል ባለስልጣናትን በመጠቀም በወለጋ እና በጉራ ፈርዳ ላይ የተደረጉት ጭፍጨፋዎችና ማፈናቀሎች በሙሉ በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የተፈፀሙ ናቸው። ይህንን እውነታ የሚያጠናክር በ1994 እና በ2007 በ13 ዐመታት ውስጥ በሀገሪቱ በዋና ዋና ክልሎች የእምነቶች አማኝ ቁጥር በፐርሰንት እንደተቀመጠው የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ  እንዳሽቆለቆለ ያሳያል።
      ከታች በቻርቱ ላይ እንደምንመለከተው በ1994 እና በ2007 በአማራው ክልል የእምነቶች አማኝ ቁጥር በ ፐርሰንት ቀርቦል፤ በ2007 የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ብዛት ከ1994  በ3% ቀንሶ ይገኛል።

     ከታች በቻርቱ ላይ እንደምንመለከተው በ1994 እና በ2007 በኦሮሚያ ክልል የእምነቶች አማኝ ቁጥር በ ፐርሰንት ቀርቦል፤ በ2007 የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ብዛት ከ1994 10.9% ቀንሶ ይገኛል።




      ከታች በቻርቱ ላይ እንደምንመለከተው በ1994 እና በ2007 በደቡብ ክልል የእምነቶች አማኝ ቁጥር በ ፐርሰንት ቀርቦል፤ በ2007 የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ብዛት ከ1994  7.7% ቀንሶ ይገኛል።



2-        ሕውሀት 90% በላይ ኦርቶዶክስ ከሚኖርበት የትግራይ ክፍለ ሀገር በመውጣቱ ባለስልጣናቱ ምንም እንኳን እምነቱ ባይኖራቸውም ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ የጥፍት እርምጃ ሊወስዱ አይችሉም የሚል አስተሳሰብ በሕዝቡ ውስጥ እንዲፈጠር  የፕሮፓጋንዳ ስራ ሰርተዋል። ባሳለፍነው 25 ዓመታት ውስጥ የተቃጠለው ቤተክርስቲያንና ገዳማት ብዛት እና በጅምላ የተጨፍጨፉት ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ብዛት ሲታይ ከሱማሌ ወይም ከሱዳን መንግስት በኩል የተፈፀመ ቢሆን ኖሮ ያለምንም ማመታት ሀይማኖታችንን ሊያጠፉ ነው ብለን እንከስ ነበር፤ ሆኖም ግን ድርጊቱ የሚፈጸመው በውስጣችን  ባሉ እና ለዛውም ስማቸው ገ/መስቀል እና ገ/ማርያም ተብለው በሚጠሩ ባለስልጣናት በመሆኑ እስከዛሬ ድረስ ክሱን አስቸጋሪ አድርጎታል።

      እውነታው ግን ከታሪክ እንደምናየው በ1600 ክፍለ ዘመን አካባቢ በአፄ ሱስንዮስ አማካኝነት ኢትዮጵያን ካቶሊክ የማድረግ ሙከራ ከከሸፈ በሆላ ካቶሊኮች ከኢትዮጵያ እንዲባረሩ ሲደረጉ አልፎንሱ የተባለው የካቶሊክ ቄስ  በኤርትራ አካባቢ ተዘዋውሮ ቅባትና ፀጋ የሚባሉ ፀረ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የምንፍቅና ትምሕርት አስተምሮ ብዙ ተከታዮችን አፍርቷል፤ ይህ እምነት አንዳንድ ጊዜ በግልጽ ሊላ ጊዜ በስውር ሲስፋፋ ቆይቶ በአፄ ቴዎድሮስ፣ በአፄ ዮሐንስ እና በአፄ ምንሊክ ጊዜ ይሕንን እምነት የሚያራምድ ካሕን ወይም ምእመን ቢገኝ ከፍተኛ ቅጣት እንደሚጠብቀው በማወጃቸው እምነቱን ከካቶሊክ ጋር ያለው ትስስር ሳይቋረጥ በሚስጥር ተዋቅሮዋል።

/የኢትዮጵያ ከአፄ ልብነ ድንግል እስከ አፄ ቴዎድሮስ/  በተክለ ጻድቅ መኩሪያ ገፅ 144

     በአንደኛው ሆነ በሁለተኛው የጣሊያን ወረራ ወቅት የዚህ እምነት ተከታዮች ካሕናትና ምእመኑ ለጣሊያን በባንዳነት አገልግለዋል። ዛሬ ሕውሀትን የፈጠሩት ሰዎች አባቶቻቸው የታወቁ ባንዳዎች እንደሆኑ ሲታወቅ አምነታቸውም ፀረ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ከሆነው አፍቃሪ ካቶሊክ ጋር የተያያዘ ነው። ቤተክርስቲያን ላይ ተሹመው ያሉ ጳጳሳትም አብዛኛዎቹ በዚሕ በሚስጥር ከሚንቀሳቀሰው አፍቃሪ ካቶሊክ አማኞች ናቸው። ለዚህም ነው በቤተክርስቲያን ላይ የሚነሱ የተሀድሶና ሊሎች የኑፋቄ ትምሕርቶችን የሚያራምዱ ግለሰቦችን ሲኖዶሱ አውግዞ እንዲለያቸው አልያም ከኑፋቅያቸው እንዲመለሱ አድርጉ ተብለው ሲጠየቁ ፍቃደኛ የማይሆኑት።


-    የኢትዮጵያ ሙስሊሞችና የሕውሀት ጠብ

        ሕውሀት የኢትዮጵያን ሙስሊሞች ለመያዝ በኦርቶዶክስ ክርስቲያን መንግስት ሲጨቆኑ እንደኖሩ አድርጎ ሲሰብክ ነበር፤ ቡዙ ሙስሊሞች ስብከቱ እውነት መስሏቻው ለረጅም ጊዜ አምነው ተቀብለውት ነበር። በእምነታቸው ሙስሊም የሆኑ የክልል ባለስልጣናት ወያኔ የሚያራምደውን የጸረ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ትግል በመደገፍ ሕዝበ ክርስቲያኑን በማፈናቀል፣ ቤተክርስቲያን እንዳይሰራ በማገድ እና ኦርቶዶክስ ክርስቲያንኖች በክልሉ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ስራ እንዳይቀጠሩ በማድረግ የወያኔን አላማ በፍቃደኝነት ሲያራምዱ ቆይተዋል።

  ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእስልምና መሪዎችን በራሱ ፍቃድ በመምረጡ በሙስሊሙ ማሕበረ ሰብ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል። ይህ ተቃውሞ እየተጠናከረ  በሀገር ውስጥ ሆነ ከሀገር ውጪ አድማሱን አስፍቷል፤ እስካሁን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እያደረጉት ያለው ተቃውሞ ሰላማዊ ሲሆን ትግላቸው በሀይል የታገዘ ቢሆን በቀላሉ ሕውሀት የሀይማኖት ነጻነት ትግላቸውን ሊላ ትርጉም በመስጠት ትግሉን ለማዳፈን አለማቀፍ ድጋፍ ያስገኝለት ነበር።

  ይህ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የእምነት ነጻነት ሰላማዊ ትግል ወደሌላ አቅጣጫ እንዳያመራ በመፍራት አንዳንድ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ስጋታቸውን በተለያየ መንገድ ሲገልጹ ይሰማል፤ ነገር ግን ይህ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን በፍጹም ስጋት ውስጥ ሊከት አይገባም ይልቅስ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ለ25 ዓመታት የሀይማኖት ነጻነታችንን ለተነጠቅንና ለተገፋን  ከኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የነጻነት ትግል በመማር እኛም ስለ ሀይማኖታችን ነጻነት ሁለገብ ትግል በተቀናጅ መልኩ ልናደርግ ይገባል።


-     የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች የነጻነት ትግል እና የፓለቲካ ስልጣን ጥያቄ

        ከላይ በተለያዩ ርእሶች እንዳየነው የሕውሀት መንግስት ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ጨቁኖና የእምነት ነጻነት አሳጥቶ እንዳለ ይታወቃል፤ ኦርቶዶክስ ክርስቲያንኖች ሕልውናቸው የሚረጋገጠው በቅድሚያ ቤተክርስቲያናችንን ከወያኔ ስርአት ታግለን ነጻ ማድረግ ስንችል ነው። ይህ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች የነጻነት ትግል ማንኛውንም አማራጭ መጠቀም የሚያስችል ይሆናል፤ የነጻነት ትግል ለማድረግ የተጨቆነው አካል ነው የነጻነት ትግሉን በምን መልክ መሆን እንደሚገባው መወሰን የሚገባው። ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች እራሳቸውን ሆነ ቤተክርስቲያናቸውን ነጻነት እንዴት መታገል እንዳለባቸው የአባቶቻቸውን ታሪክ ማወቅ ይኖርባቸዋል።

      ሊላው በአለማችን ላይ ሕዝቦች ሀይማኖታቸውን መሰረት አድርገውና ተደራጅተው ለዲሞክርሲያዊ የፖለቲካ ስልጣን ይወዳደራሉ። በተለይ በአደጉና ዲሞክራት ሀገራት በሀይማኖት ማንነታቸው የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደሉም። ለምሳሌ፦

·         Germany- (ገዥው) Christian democratic union of Germany, Christian social union in Bavaria.

·         Netherlands- Christian democratic appeal, Christian union.

·         Russia- Christian democratic party of Russia.

·         United States- Christian democratic union of the United States.

·         United Kingdom- Christian Democratic Party, Christian Party, Christian People’s Alliance, The Common Good (Political Party).

አነዚህ ከላይ ለምሳሌ ያየናቸው ሀገራት በሀይማኖታቸው የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዋች ለስልጣን እንዲወዳደሩ ሕገመንግስታቸው ያዛል። አሁን ያለው የወያኔ ሕገመንግስት በቋንቋ ማንነት ላይ የተደራጁ ፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ስልጣን እንዲመጡ ሲፍቅድ ከላይ እንዳየነው በየትኛውም የዲሞክራሲ ሀገራት የሚፈቀደውን በሀይማኖት ማንነት ለፖለቲካ ስልጣን መደራጀትን ወያኔ በሕገ መንግስቱ አንቀጽ11 እና 27 ላይ አግዶታል።

 የኢትዮጵያ ሕዝብ ከየትኛውም የአለም ሕዝብ በተሻለ ሀይማኖተኛ ሕዝብ ነው፤ ታሪኩም እንደሚያሳየው ኢትዮጵያን ይገዙ የነበሩት ነገስታት ከማንኛውም ማንነት የሀይማኖት ነገር ከፍተኛውን ቦታ ይይዛል። በኢትዮጵያ ሀይማኖቶች ወደ ፖለቲካ ስልጣን መምጣት አሁን በማን አለብኝነት ተወጥሮና ገዝፎ የሚታየውን ከቋንቋ ማንነት አልፎ ወደዘርና ቢሔር የተቀየረውንና ሀገራችንን አደጋውስጥ የጣለው ፓለቲካ የሚያስተነፍስ ይሆናል።

       በሕውሀት የረቀቀው የሀገሪቱ ሕገመንግስት በዓለም ላይ ዋና ከሆነው የዲሞክራሲ መርሆች አንዱ የሆነው  በዲሞክራሲያዌ መንገድ በነጻነት በተለያየ መንገድ  የመደራጀትን መብት በጣሰ መልኩ የሀይማኖት ማንነትን መሰረት አድርጎ ለፖለቲካ ስልጣን መደራጀትን የሚከለክል ሕግ ደንግጓል።  ይህ ሕግ በአለም ላይ ባሉ ዲሞክራቲክ ሀገራት ላይ የማይሰራ መሆኑን ለአብነት ከላይ ለምሳሌነት የቀረቡ ሀገራትን ማየት ይቻላል። ሕውሀት አስቀድሞ ይህንን ነጻነት የነፈገበት ምክንያት ኢትዮጵያውያን ለእምነታቸው ያላቸውን ትልቅ ክብር በመረዳት በእምነት ለፖለቲካ ስልጣን መደራጀት እነሱ የመጡበትን ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፖለቲካን ተቀባይነት እንደሚያሳጣው አስቀድመው ስለተረዱ ነው።

       አሁን በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ከወያኔ የጭቆና ስርአት ነጻ ለመውጣት አለማቀፋዊ በሆነው የዲሞክራሲ መርሕ  በነጻነት ለፖለቲካ ስልጣን መደራጀት መብታቸው እንደሆነ አውቀው ሕውሀት በሀገሪቱ ሕገመንግስት ላይ አደናብሮ ያስቀመጠውን ሀይማኖት በፖለቲካ ውስጥ ያለመግባት ሕግ በመቃወም እንዲነሳ እና በሀገራችን ዲሞክራሲያዊ ስርአት እንዲሰፍን መታገል ይኖርባቸዋል።

  


   


Sunday, August 21, 2016

ሰማእትነትን ከሸሹት ሰማእት ሊኖር አይችልም


        አንዳንድ ሰባክያን ጥንት እንጂ አሁን ሰማእትነት የለም እያሉ ያስተምራሉ፡፡ ሰባክያኑ ቄሳርን ፈርተው ቄሳርን የማያስቆጣ ነገር ካልተናገሩ በየት ሰማእትነት ያገኛቸዋል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀገሩ ከልዳ ተነስቶ ፋርስ ድረስ ሄዶ የአንድ ሳይሆን የሰባ ነገስታትን ግርማ ሳይፈራ በጀግነት ስለሀይማኖቱ ስለመሰከረ ከሰማእታት ሁሉ የበለጠ የሰማእትነት ክብር አግኝቷል፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥም ሰማእትነት አለ ክርስቲያኖች በሰይፍ ይታረዳሉ፣ በእሳት ይቃጠላሉ፣ ከቀያቸው ይፈናቀላሉ ንብረታቸውን ይዘረፋሉ  ታድያ ይህንን በአይናቸው እያዩ ሽምጥጥ አድርገው ዛሬ ሰማእትነት የለም ከራስ ጋር መታገል ነው እያሉ በድፍረት ይናገራሉ፡፡

          በ17ተኛው ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ ታሪክ የኢትዮጵያ ንጉስ የነበሩት አጼ ሲስንዮስ የተዋህዶ እምነታቸውን ቀይረው ካቶሊክ ሲሆኑና የካቶሊክን እምነት በኢትዮጵያ ለማስፋፋት ሲሞክሩ ይህንን ስራቸውን የተቃወሙ ‹‹ አንተ በኢትዮጵያ ምድር እውነተኛውን እምነት ትተህ የባእድ እምነት አምነህ በኢትዮጵያ ላይ መሪ አትሆንም›› ብለው በመቃወማቸው ካህናቱ፣ ጳጳሱ፣ ምእመናኑ፣ እና መኳንንቱ በሰማእትነት አልፈዋል፡፡ እነሱ በከፈሉት ሰማእትነት ቤተክርስቲያን ህያው ሆና እስካሁን ደርሳለች፡፡

        አሁን በኢትዮጵያ ካቶሊክ አይደለም እግዚአብሔርን የማያምን (ፓጋን) መሪ ተቀምጦ ደሐ ሲበድል፣ ክርስቲያኖችን ሲያሳድድ፣ ቤተክርስቲያንን ሲያስቃጥል፣ የቤተክርስቲያንን ንብረት ቅርስ ሲያዘርፍ፤ ጳጳሳቱ፣ ሰባክያኑ  ካልተናገሩና ካልተቃወሙ ከየት ሰማእትነት ይመጣል፡፡ እስካሁን እንዳየነው ምእመናኑ እና ካህናቱ ታረዱ፣ ተገደሉ፣ ከቀያቸው ተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው ተዘረፈ፣ ፍርድ ተጓደለባቸው ሲባል ሰምተናልም አይተናልም ፡፡ ነገር ግን  አንድም ጳጳስ እና ሰባኪ ታሰረ፣ ተገደለ ተብሎ ሲናገርም አልሰማንም አላያንም ሊላው ቀርቶ በስደት ያሉት ሰባክያን ኢትዮጵያ ውስጥ ስላላቸው ንብረት እና ቤተሰቦቻቸው እያሰቡ ስለ ቄሳር ማንሳት አይፈልጎም፡፡

        ንጉስ አክሀብ የደሀውን የናቡቴን መሬት ለመውረስ የናቡቴን ደም አፈሰሰ፡፡ የእግዚአብሔር ሰዎች የደሀው ደም ሲፈስ ዝም ብለው አያዩምና በወቅቱ ነብይ የነበረው የእግዚአብሔር ሰው ኤልያስ ተነስቶ ንጉሱን አክአብን ተቃወመው፡፡ ስላደረገውም በደል በሱ ላይ ተመሳሳይ ቅጣት እደሚያገኘው ነግሮታል፡፡ ዛሬ በሀገራችን ደሀው በችግር ተቆራምዶ፣ ቤቱ ንብረቱ መሬቱ እየተወረሰ፣ ፍርድ አቶ የዳኛ ያለህ እያለ፤ ያም ሳይበቃ እንደ ራሔል እናት  ልጆቿን በቄሳር ወታደሮች ተገለውባት እምባዋን ወደ ራማ በምትረጭበት ወቅት ጳጳሳቱና ሰባክያኑ በህዝቡ ገንዘብ ኑሮዎቸውን እየደጎሙ ይልቁንም ቄሳርን እያመሰገኑና ሰማእትነት የለም ሁሉም ሰላም ነው እያሉ ተቀምጠዋል፡፡ ይዘገያል እንጂ የደሀው ጭሆት የናቶች እንባ ጽዋው ሞልቶ ወደ እግዚአብሔር ደርሶ መልስ ይዞ መምጣቱ አይቀርም፡፡ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት እንጀራ ያደረጉት ጳጳሳትና ሰባክያን የት ይደርሱ ይሆን፡፡

        

Wednesday, July 13, 2016

ወዮ ለትግራይ!


ወዮ ለትግራይ!

             በትግራይ መንገዶች እየተመላለሳችሁ ሩጡ ተመልከቱም እወቁም በአደባባይዋም ፈልጉ ፍርድን የሚያደርገውን እውነትንም የሚሸውን ሰው ታገኙ እንደሆነ ይቅር እላታለሁ። እነርሱም ሕያው እግዚአብሔርን! ቢሉ የሚምሉት በሐሰት ነው። አቤቱ ዓይንህ እውነትን የምትመለከት አይደለችምን? አንተ ቀሰፈሃቸዋል ነገር ግን አላዘኑም ቀጥቅጠሃቸዋል ነገር ግን ተግሣጽን እንቢ አሉ ፊታቸውን ከድንጋይ ይልቅ አጠንክረዋል ይመለሱ ዘንድ እንቢ አሉ።

          እኔም የእግዚአብሔርን መንገድ የአምላካቸውን ሕግ አላወቁምና እነዚህ በእውነት ድሆችና ሰነፎች ናቸው፤ ወደ ታላላቆቹም ካሕናትና ጳጳሳት እሄዳለሁ አናገራቸውማለሁ የእግዚአብሔርን መንገድ የአምላካቸውን ሕግ ያውቃሉና አልሁ። አነዚህ ግን ቀንበሩን በአንድነት ሰብረዋል እስራቱንም ቆርጠዋል። ስለዚህ ሀጢአታቸው በዝቶአልና የክዳታቸውም ብዛት ጸንቶልና ስለዚህ አንበሳ ከዱር ወጥቶ ይሰብራቸዋል የበረሀም ተኩላ ያጠፋቸዋል ነብርም በከተማቸው ላይ ይተጋል ከዚያም የሚወጣ ሁሉ ይነጠቃል።

          ትግራይ ሆይ በእነዚህ ነገሮች ይቅር የምልሽ እንዴት አድርጌ ነው? ልጆችስ ትተውኛል አማልክትም ባልሆኑ ምለዋል ካጠገብሀቸው በሗላ አመነዘሩ በጋለሞቶችምቶቹም ቤት ተሰበሰቡ። እንደ ተቀለቡ ፈረሶች ሆኑ፤ እያንዳንዳቸውም ከባልንጀሮቻቸው ሚስቶች ሗላ አሽካኩ። በውኑ ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀሥፍምን? ይላል እግዚአብሔር ነፍሴስ እንደዚህ ባለ ሕዝብ ላይ አትበቀልምን? የትግራይ ልጆች እጅግ ወንጅለዋል ይላል እግዚአብሔር። እነሱም ክፉ ነገርም አይመጣብንም ሰይፍንና ራብንም አናይም።

          ስለዚህም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ትግራይ ሆይ እነሆ ሕዝብን ከሩቅ አመጣባችሀለው ፣ ሀያል ጥንታዊ ሕዝብ ነው ቋንቋቸውንም የማታውቀው የሚናገሩትንም የማታስተውለው ሕዝብ ነው። የሰይፋቸውም ሰገባ እንደተከፈተ መቃብር ነው፣ ሁሉም  ሀያላን ናቸው። መከርህንና እንጀራህን ይበላሉ፣ ወንዶችና ላሞችህንም ይበላሉ በለስህንም ይበላሉ የምትታመናቸውን የተመሸጉ ከተሞችን በሰይፍ ይደበድባሉ። እንዲህ ይሆናል እናንተ አምላካችን እግዚአብሔር ይህን ነገር ሁሉ ስለምን አደረገብን ብትሉ እናንተ እደተዋችሁኝ በአገራችሁም ሌሎችን አማልክት እንዳመለካችሁ እንዲሁ ለእናንተ ባልሆነ አገር ለሌሎች ሰዋች ትገዛላችሁ።

         እናንተ ሰነፎች ልበ ቢሶች ዓይን እያላችሁ የማታዩ ጆሮም እያላችሁ የማትሰሙ የትግራይ ሕዘብ ሆይ ይህን ስሙ። በውኑ እኔን አትፈሩምን? ከፊቴስ አትደነግጡም ? ይላል እግዚአብሔር ። በናተ መካከል ክፉዎች ሰዎች ተገኝተዋል እንደ አጥማጆችም ያደባሉ ወጥመድንም ይዘረጋሉ ሰዋችንም ያጠምዳሉ። ቀፎ ወፎችን እንደሚሞላ እንዲሁም ቤታቸው ሽንገላን ሞልታለች፤ እንዲሁም ከብረዋል ባለጠጎችም ሆነዋል ወፍረዋል ሰብተውማል ክፋታቸውንም ያለ ልክ አብዝተዋል የድሀ አደጎች ነገር መልካም ፍርድ አልፈረዱላቸውም። በውኑ ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀስፍምን? ይላል እግዚአብሔር ነፍሴስ እንደዚህ ባለ ሕዝብ ላይ አትበቀልምን?

         የምታስደንቅና የምታስደነግጥ ነገር በምድር ላይ ሆናለች ጳጳሳት በሐሰት ይናገራሉ ካህናትም በእነዚህ እጅ ይገዛሉ ሕዝቡም እንዲህ ያለውን ነገር ይወዳሉ ከፍጻሜውስ ምን ታደርጋላችሁ? እናንተ የትግራይ ልጆች ክፉ ነገር ታላቅም ጥፋት ከሰሜን ይጎበኛልና ከትግራይ ሽሹ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ ዛፎቿዋን ቁረጡ በከተማ አፈርን ደልድሉ ትግራይ የምትቀሰፍ ናት መካከልዋ ሁሉ ግፍ ብቻ  ነው። ከጉድጓድ ውሃ እንደሚፈልቅ እንዱሁ ክፋትዋ ከእርስዋ ዘንድ ይሰማል ደዌና ቁስልም ሁልጊዜ በፌቴ አለ። ትግራይ ሆይ ነፍሴ ካንች እንዳትለይ አንችንም ባድማና ወና እንዳላደርግሽ ተግሣጽን ተቀበይ።

         ትሰማኝ ዘንድ ለማን እናገራለሁ ? ለማንስ አስጠነቅቃለሁ? እነሆ ጆሮአቸው ያልተገረዘች ናት ለመስማትም አይችሉም እነሆ የእግዚአብሔር ቃል ለስድብ ሆኖባቸዋል ደስም አያሰኛቸውም ። ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ስስትን ያስባሉና፤ ከጳጳሳት ጀምሮ እስከ ካህናት ድረስ ሁሉ በተንኮል ያደርጋሉና። ሰላም ሳይሆን ሰላም ሰላም ይላሉ። ርኩሰት ነገር ስለ ሠሩ አፍረዋልን? ምንም አላፈሩም እፍረትንም አላወቁም ስለዚህ ከሚወድቁ ጋር ይወድቃሉ በጎበኘሀቸው ጊዜ ይዋረዳሉ ይላል እግዚአብሔር።

        እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመች የአባቶቻችሁን መንገድ ጠይቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች እወቁ በእርስዋም ላይ ሂዱ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ እነርሱ ግን አንሄድባትም አሉ።

         እነሆ በዚህ ሕዝብ ፊት እንቅፋቶችን አደርጋለሁ አባቶችና ልጆች በአንድነት ይሰናከሉባቸዋል፣ ጎረቤትና ባልንጀራም ይጠፈሉ። እነሆ ሕዝብ ከሰሜን አገር ይነሣል ቀስትንና ጦርን ይይዛሉ ጨካኞች ናቸው። ምሕረትም አያደርጉም ድምፃቸው እንደ ባሕር ይተማል በፈረሶችም ላይ ይቀመጣሉ፤ የትግራይ ሴት ሆይ ማቅ ልበሺ በአመድም ውስጥ ተንከባከይ አጥፊ በላይሽ በድንገት ይመጣል በአንድያ ልጅ እንደሚደረግ ልቅሶ መራራ ልቅሶ አልቅሺ።

         የትግራይ ሕዝብ ሆይ እነሆ በማትረቡበት በሐሰት ቃል ታምናችሀል፤ ትሰርቃላችሁ ትገድላላችሁ ታመነዝራላችሁ በሐሰትም ትምላላችሁ የማታውቋቸውንም እንግዶች አማልክት ትከተላላችሁ መጥታችሁም ስሜም በተጠራበት በዚህ ቤት በፌቴ ቆማችሁ ይህን አስጸያፊ የሆነ ነገርን ሁሉ አላደረግንም አላችሁ። ይህስ ስሜ የተጠራበት ቤት በዓይናችሁ የሌቦች ዋሻ ሆኖአልን? እነሆ አይቻለሁ ይላል እግዚአብሔር።

        የዚህም ሕዝብ ሬሳ በሰማይ ወፎችና ለምድር አራዊት መብል ይሆናል የሚያስፈራራቸውም የለም። ምድሪቱም ባድማ ትሆናለችና ከትግራይ ከተሞች አደባባይ የእልልታን ድምፅና የደስታን ድምፅ የወንድ ሙሽራን ድምፅና የሴት ሙሽራ ድምፅ አጠፋለሁ።

         እግዚአብሔር እንዲህ ይላል የወደቁ አይነሱምን? የሳተስ አይመለስምን? እንግዲህ ይህ የትግራይ ሕዝብ ዘወትር ስለ ምን ወደ  ሗላው ይመለሳል? ተንኮልን ይዞአል ሊመለስም እንቢ ብሎአል። አዳመጥሁ ሰማሁም ቅንን ነገር አልተናገሩም ማናቸውም ምን አድርጌለሁ? ብሎ ከክፋቱ ንሰሐ የገባ የለም ወደ ሰልፍም እንደሚሮጥ ፈረስ እያንዳንዱ በየመንገዱ ይሄዳል። ሽመላ በሰማይ ጊዜዋን አውቃለች፣ ዋኖስና ጨረባ፣ ዋልያም የመምጣታቸውን ጊዜ ይጠብቃሉ፤ የትግራይ ሕዝብ ግን የእግዚአብሔርን ፍርድ አላወቀም።